Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በምዕራብ ግዳጅ ቀጠና ተልዕኮውን እየፈፀመ ያለው የሠራዊት ክፍል የሚቃጡ ትንኮሳዎችን መመከት የሚያስችል አስተማማኝ ዝግጁነት መፍጠሩ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ ግዳጅ ቀጠና ተልዕኮውን እየፈፀመ ያለው የሠራዊት ክፍል ከውስጥም ይሁን ከውጭ በኢትዮጵያ ላይ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን መመከትና መቀልበስ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አስተማማኝ ዝግጁነት መፍጠሩን የዕዙ ምክትል አዛዥ ተናገሩ።
ጀነራል መኮንኑ እንደገለጹት÷በአውደ ውጊያ አሸናፊ ሆኖ ለመውጣት በየ ደረጃው ያለ አመራር ቅንጅት፣ ቁርጠኝነትና ጠንካራ አመራር ሰጪ መሆን የማይተካ ሚና አለው፡፡
ጠላት ሀገርና ሕዝብን ሊያዋርድ አቅሙን አሟጦ ሲፍጨረጨር በመጠንከራችን ጠላትን ከፍላጎቱ በታች ማድረግ ችለናል ያሉት ምክት አዛዡ÷ በዚህ ሂደት በየ ደረጃው ያለ አመራር ሚና የማይተካ እንደነበር በመጥቀስ አመራሮች አቅማቸውን በቀጣይነት አዳብረው የክፍሎቻቸውን አቅም በማሳደግ ለተሻለ ግዳጅ ማዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አመራሮች የሚመሩትን ሠራዊት የማድረግ አቅምና የዝግጁነት ደረጃ ለማሳደግ የሚያግዙ የመሪነት ክህሎትን የሚያዳብሩ ተግባራትን ማከናወን እንዳለባቸው ማመላከታቸውን የመከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version