የሀገር ውስጥ ዜና

በደሴ ከተማ ከ250 ሚሊየን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት በቁ

By Feven Bishaw

July 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደሴ ከተማ አስተዳደር ከ250 ሚሊየን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን የአስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡

ለአገልግሎት የበቁት በደሴ ከተማ ከ1 ቢሊየን ብር በሚበልጥ ወጪ ሲካሄዱ ከቆዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ውስጥ መሆናቸውን የመምሪያው ምክትል ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር አብዱልከሪም ሀብታሙ ገልጸዋል።