የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ላይ የተከፈተው የመረጃ ጦርነት በሳይበር ደህንነትና ሌሎችም ተቋማት የጋራ ጥረት እየተመከተ ነው- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

By Feven Bishaw

July 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ላይ የተከፈተው የመረጃ ጦርነት በሳይበር ደህንነትና ሌሎችም ተቋማት የጋራ ጥረት እየተመከተ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሣ÷ መንግሥት ጦርነቱን ለመመከትና ሕግ ለማስከበር ብርቱ ጥረት እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፥ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ያስረዱት።