የሀገር ውስጥ ዜና

የመዲናዋን የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር በዘላቂነት የሚፈታ ፕሮጀክት ጥናትና ዲዛይን ተጠናቀቀ

By Feven Bishaw

July 21, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባን የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር በዘላቂነት እንደሚፈታ የታመነበት ፕሮጀክት ጥናት እና ዲዛይን መጠናቀቁን የከተማዋ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

ከፋና ብሮድካስቲን ግኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዘሪሁን አባተ÷ ፕሮጀክቱ አንድ ቢሊየን ዶላር ወጪ የሚጠይቅ ነው ብለዋል።