Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሶማሊላንድ ሉዓላዊነቴን ተጋፍቷል በሚል “ቢቢሲ”ን ከሥራ ማገዷተሰማ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሶማሊላንድ ቢቢሲ የግዛቴን ሉዓላዊነት ተጋፍቷል በሚል ሥራውን እንዲያቆም መወሰኗን አስታወቀች፡፡

የሶማሊላንድ ማስታወቂያ ሚኒስትር ሳሌባን ዩሱፍ አሊ ኮሬ በሀርጌሳ በሰጡት መግለጫ ÷ ቢቢሲ ለ30 ዓመታት ራሷን ችላ ለቆመችው ዴሞክራሲያዊ ግዛት ዕውቅና አልሰጠም ብለዋል።

ከዛሬው ዕለት ጀምሮም ቢቢሲ በግዛቷ የሚሠራቸውን ሥራዎች እንዲያቆም መወሰኑን ነው የገለጹት፡፡

ሚኒስትሩ ÷ ጣቢያው የሚያሰራጫቸው መረጃዎች ለሶማሊላንድ ሕዝብ ጆሮ እንደማይመጥኑም አስገንዝበዋል፡፡

በፈረንጆቹ 1991 በሶማሊያ ተቀስቅሶ በነበረው የእርስ በርስ ጦርነት ሶማሊላንድ ከሶማሊያ ነጻ መሆኗን እንዳወጀች ዘ ኢስት አፍሪካን በዘገባው አስታውሷል ፡፡

ስለ እገዳው ከቢቢሲ የተሰጠ አስተያየት አለመኖሩ ተመላክቷል፡፡

ከእሲያ ሀገራት ውስጥም ቻይና ባሳለፍነው ዓመት ቢቢሲን ከስራ ማገዷ ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version