አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጨፌ ኦሮሚያ 6ኛ የሥራ ዘመን 1ኛ አመት 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡
ጨፌው የ2014 የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት በማዳመጥ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
እንዲሁም በ2015 እቅድ ዙሪያ በመወያየት ቀጣይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ፤ በጀትም ያፀድቃል መባሉን ኦቢኤን ዘግቧል፡፡
የጨፌው መደበኛ ስብሰባም ለሁለት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ የወጣው መርሐ ግብር ያመለክታል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!