በአዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 2ኛ ቀኑን ባስቆጠረው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ከተሳተፉት ሶስት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሁለቱ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡
በመጀመሪያው ምድብ የወርቅውኃ ጌታቸው 2ኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ፍፃሜ ማለፍ ስትችል መቅደስ አበበ በሁለተኛው ምድብ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ፍጻሜ ማለፏን አረጋግጣለች፡፡
በሶስተኛው ዙር የተሳተፈችው ሲምቦ አለማየሁ 5ኛ ደረጃን ይዛ ርቀቱን በመጨረሷ ከውድድሩ ውጪ ሆናለች።
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!