Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ የዶራሌህ የእንስሳት ማቆያ ተርሚናልን ጥቅም ላይ ለማዋል ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ የዶራሌህ የእንስሳት ማቆያ ተርሚናልን ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡

ተርሚናሉ ኢትዮጵያ በእንስሳት ሀብት ቀዳሚ ሀገር እንደመሆኗ ሀብቷን በተገቢው መልኩ ወደ ውጭ እንድትልክ በማስቻል እና የውጭ ምንዛሪ ገቢ በማስገኘት ከእንስሳት ሀብቷ ተጠቃሚ እንድትሆን ያስችላታል ተብሏል፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱን የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ኡመር ሁሴን እና የጂቡቲ አቻቸው ሙሀመድ አሕመድ መፈረማቸውን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል ፡፡

አቶ ኡመር ሁሴን ጉዳዩን አስመልክቶ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ የዶራሌህ ሁለገብ ወደብ ወደ ስራ መግባቱ፥ ወደ ውጭ ለሚላኩ እንስሳት የማረፊያ ተርሚናል ሆኖ በማገልገል እና የቀጥታ ግብይትን በማበረታታት የኢኮኖሚ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

 

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version