አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አየርላንድ በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ እርዳታ የሚውል ተጨማሪ አንድ ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ አደረገች፡፡
አየርላንድ ያደረገችው ድጋፍ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ችግር ውስጥ ለሚገኙ እና አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሚውል መሆኑ ተገልጿል፡፡
በዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ማህበር በኩል የሚሰራጨው ይህ ድጋፍ÷ በኢትዮጵያ የሚደረገውን የሰብአዊ እርዳታ ምላሸ ለማሳደግ እንደሚያስችል ከአየርላንድ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡