የሀገር ውስጥ ዜና

የኢድ አል አድሀ በዓልን በማስመልከት ለ1 ሺህ 800 ወገኖች የማዕድ ማጋራት ስነ ስርዓት ተካሄደ

By ዮሐንስ ደርበው

July 10, 2022

ስነ-ስርዓቱ በካሊድ ፋውንዴሽን ምግባረ ሰናይ ድርጅት የተከናወነ ሲሆን÷ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬን ጨምሮ ወንድም ካሊድ እና ሌሎች አካላት ተገኝተዋል፡፡

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በዚሁ ወቅት÷ኢትዮጵያና ህዝቦቿ በበርካታ ውስብስብ ችግሮች ውስጥ እያለፉ ቢሆንም እናቶቻችንና አባቶቻችን ያወረሱንን መተባበር፣ መደማመጥ፣ መከባበር እና መተዛዘን አጠናክረን ከቀጠልን የማንሻገረው ፈተና እንዳማይኖር የዛሬው የአብሮነት ስነ-ስርዓት ህያው ምስክር ነው ብለዋል፡፡

የዘንድሮ የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓልን በማስመልከት የማዕድ ማጋራት ስነ ስርዓት እንዲሳካ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና ያቀረቡት ወንድም ካሊድ በበኩላቸው÷ ስነ-ስርዓቱ ለሶስት ቀናት እንደሚቆይ ገልጸዋል፡፡

ከኢድ እስከ ኢድ ጥሪ ዋና ዓላማው ዳያስፖራው ሀገሩን እንዲያውቅና እንዲያስተዋውቅ እንዲሁም ወገኑን በሀሳብና በሌሎች  እንዲደግፍ ነው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሀመድ እንድሪስ ናቸው፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-