Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኮንጎ እና ሩዋንዳ ጸባቸውን አርግበው ግንኙነታቸውን ወደ ቀድሞው ለመመለስ ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ሩዋንዳ በመካከላቸው የተፈጠረውን ውጥረት ለማርበብ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ወደ ቀድሞው ለመመለስ ተስማምተዋል፡፡

ሀገራቱን በሩዋንዳ ያሸማገሉት የአንጎላው ፕሬዚዳንት ጆአዎ ሎሬንኮ ሲሆኑ ፥ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለቆየው ጠላትነት በፍጥነት መፍትሄ ለመሥጠት ሁለቱ ወገኖች መሥማማታቸውን አስታውቀዋል።

የተሸመገሉት የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ቲሺሴኬዲ እና የሩዋንዳው ፖል ካጋሜ መሆናቸውንም ዘ ኢስት አፍሪካ ዘግቧል፡፡

አንጎላ በሚቀጥለው ማክሰኞ የሩዋንዳ-ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሁለትዮሽ የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ እንደምታስተናግድ በአፍሪካ ኅብረት የተሾሙት አሸማጉዩ የአንጎላ ፕሬዚዳንት ጆአዎ ሎሬንኮ ተናግረዋል፡፡

ሎሬንኮ የዓለምአቀፉ የታላላቅ ሐይቆች ቀጣና ጉባዔ ሊቀ መንበር መሆናቸውም ይታወቃል፡፡

ሩዋንዳ እና ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አማጺያን ቡድኖችን ትደግፋለች በሚል እርስ በእርስ በጠላትነት ሲፈራረጁ እና ሲወነጃጀሉ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version