አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራል ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታና ደህንነት አካላት ጋር በመቀናጀት 1 ሺህ 443ኛው ዒድ አል አድሃ /አረፋ/ በዓል በሰላም እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ፡፡
የእስልምና እምነት ተከታዮች በዓሉ በሰላም እንዲከበር ከፀጥታና ደህንነት አካላት ጎን በመቆም የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጥሪ አቅርቧል፡፡
በተጨማሪም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1 ሺህ 443ኛው ዒድ አል አድሃ /አረፋ/ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላፏል።
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!