Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የዶዶላ ኢፋ ቦሩ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤትን መረቁ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ ከ350 ሚሊየን ብር ላይ በሆነ ወጪ የተገነባውን የዶዶላ ኢፋ ቦሩ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት መርቀዋል፡፡
በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ እንደተገለጸው÷ ትምህርት ቤቱ ከሀገር ውስጥ ቋንቋዎች በተጨማሪ በቻይንኛ፣ ፈረንሳይኛ እና በዓረብኛ ቋንቋዎች ያስተምራል፡፡
ዘመናዊ የ አይ ሲ ቲ ላቦራቶሪ፣ ኮምፒውተር እና ወርክሾፕ ክፍሎች የተሟሉለት መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም ተማሪዎቹ የሚዝናኑበት መዋኛ ገንዳ ፣ አምፊ ቴአትር ቤት፣ ቴኒስ ኳስ፣ ቅርጫት ኳስ፣ መረብ ኳስ፣ ቼዝ እና ቴኳንዶ የሚሰሩበት ዘመናዊ ጂምናዚዬም ማካተቱን ኦቢኤን ዘግቧል፡፡
ትምህርት ቤቱ የሚገለገልበት የእንስሳት ማርቢያ እንዳለውም ተገልጿል፡፡
በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ የተገነባው የዶክተር ኃይሌ ፊዳ መታሰቢ ሐውልትም ተመርቋል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version