Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ክለቦች የዝውውር መስኮት ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ክለቦች የ2015 ዓ.ም የውድድር ዘመን የመጀመሪያው የዝውውር መስኮት ዛሬ ተከፍቷል።

የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ዛሬ ሲከፈት ኢትዮጵያ ቡና ሁለት ተጫዋቾቹን የግሉ ማድረጉን አስታውቋል።

ቡናማዎቹ የአማካይ መስመር ተጫዋቹን አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ እና የግራ መስመር ተከላካዩ ኃይለሚካኤል አደፍርስን ከሰበታ ከተማ አስፈርመዋል።

ተጫዋቾቹ በክለቡ ለሦስት ዓመታት የሚያቆያቸውን ውል ፈርመዋል።

የክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን እስከ መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ከኢትዮጵያ ከእግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version