Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዓለም የምግብ ፕሮግራም በአፋር ክልል ከ650 ሺህ በላይ ተረጂዎች ዕርዳታ ማከፋፈሉን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የምግብ ፕሮግራም በአፋር ክልል በግጭት እና በድርቅ ለተጎዱ ከ650 ሺህ በላይ ወገኖች የምግብ ዕርዳታ ማከፋፈሉን አስታውቋል፡፡

ዕርዳታውን ወደ ክልሉ ያደረሰው በየስድስት ሣምንታት ልዩነት በማጓጓዝ መሆኑን ጠቁሟል።

ባለፈው ሳምንትም ለ80 ሺህ ወገኖች በምግብ አቅርቦት ተደራሽ መሆን እንደቻለ በትዊተር ገጹ አስታውሷል፡፡

በዛሬው ዕለትም የድርጅቱን የአስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች በሰሜናዊ አፋር ኮኔባ አካባቢ ደርሰው አቅርቦቱን መጋዘን ውስጥ እያራገፉ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version