Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአፍሪካ አየር መንገዶች በነዳጅ ዋጋ መናር 4 ቢሊየን ዶላር እንደሚያጡ ተነገረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በተያዘው ዓመት የአፍሪካ አየር መንገዶች በነዳጅ ዋጋ መናር ምክንያት ማግኘት የነበረባቸውን 4 ቢሊየን ዶላር ገቢ እንደሚያጡ የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር ገልጿል፡፡

የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ተከትሎም የኬንያ አየር መንገድ የበረራ ክፍያውን እንደገና ለመከለስ እንደሚገደድ ነው ማኅበሩ ያመላከተው፡፡

የአፍሪካ አየር መንገዶች በተያዘው ዓመት የሚያጡት የ4 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ገቢ በፈረንጆቹ 2019 ላይ ካስገቡት ገቢ 23 ነጥብ 4 በመቶ ያህሉን እንደሚሆን መገለጹንም ዘ ኢስት አፍሪካ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version