በአዲስ አበባ ከተማ በ40/60 እና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለ25 ሺህ 491 ቤቶች ነገ ዕጣ ይወጣባቸዋል

By Melaku Gedif

July 06, 2022

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች ባለፉት የቤት ልማት ፕሮግራም ከጀመረበት አንስቶ በ17 ዓመታት ውስጥ ለህብረተሰቡ ማቅረብ የተቻለው 300 ሺህ ያህል ቤቶችን ብቻ መሆኑን ገልፀዋል።

አሁንም በሚወጡት ውስን ቁጥር ያላቸው ቤቶች የህብረተሰቡን ችግር መቅረፍ ስለማይችሉ ከተማ አስተዳደሩ አምስት አይነት የቤት ልማት አማራጮችን መዘርጋቱን አስታውቀዋል፡፡