Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የ2014 የበጀት ዓመት የሴክተር መስሪያ ቤቶች ዕቅድ አፈፃፀም እየገመገመ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) የ2014 የበጀት ዓመት የሴክተር መስሪያ ቤቶች እቅድ አፈፃፀም እየገመገመ ይገኛል።
በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሚስራ አብደላን ጨምሮ የካቢኔው አባላት ተገኝተዋል።
በግምገማ መድረኩም÷ በዓመቱ በሴክተር መስሪያ ቤቶች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን በሚመለከት በክልሉ ፕላንና ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሪፖርት ቀርቧል።
ውይይቱ በነገው ዕለትም ቀጥሎ እንደሚካሄድ የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version