የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ሽመልስ አብዲሳ በሮቤ ከተማ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መረቁ

By ዮሐንስ ደርበው

June 29, 2022

የአብዲ ቦሩ የሕጻናት ትምህርት ቤት ዛሬ ከተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ሲሆን÷ በ412 ነጥብ 9 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ወጪ የተገነባ ነው፡፡

ትምህርተ ቤቱ 6 ብሎኮች ያሉት ሲሆን÷ 333 ሕጻናትን ተቀብሎ የማስተማር አቅም እንዳለው ተገልጿል፡፡

በዛሬው ዕለት ከተመረቁት ፕሮጀክቶች በ1 ነጥብ 6 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የተገነባው የመደ ወላቡ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንዱ ሲሆን÷ 24 ክፍሎች ያሉት እና 2 ሺህ 200 ተማሪዎችን የማስተማር አቅም እንዳለው ተገልጿል፡፡

 

በተመሳሳይ በ21ሚሊየን ብር የተገነባው የጀነራል ዋቆ ጉቱን ሐውልት የያዘው አደባባይ ተመርቋል።