የሀገር ውስጥ ዜና

ጠርዝ የረገጡ ሐሳቦች ወደ መሀል እንዲመጡ እና ዜጎች እንዲተባበሩ ማድረግ ይገባል – የሃይማኖት መምህራን

By Feven Bishaw

June 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠርዝ የረገጡ ሀሳቦች ወደ መሀል እንዲመጡ እና ዜጎች እንዲተባበሩ ማድረግ እንደሚገባ የተለያዩ የሃይማኖት መምህራን ገለጹ፡፡

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉ የተለያዩ ሃይማኖቶች መምህራን ጠርዝ የረገጡ ሀሳቦች ወደ መሀል እንዲመጡ እና ዜጎች እንዲተባበሩ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመው÷ ለዚህ ዓላማም የሃይማኖት አባቶች ኃላፊነት ከፍ ማለት ይገባዋል ብለዋል፡፡