የሀገር ውስጥ ዜና

የካፋ ዞን በ58 ሚሊየን ብር ወጪ የገዛቸውን የእርሻ ትራክተሮች ለወረዳዎች አከፋፈለ

By Feven Bishaw

June 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የካፋ ዞን አስተዳደር የዞኑን አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሚያስችሉ 25 ትራክተሮችን ለወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች አከፋፍሏል፡፡

የእርሻ የሜካናይዜሽን እርሻ ለማስፋፋት ያግዛሉ የተባሉት የእርሻ ትራክተሮቹ ከ58 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገባቸውና ወጪውም በዞኑ መንግስት በኩል እንደተሸፈነ ተገልጿል።