የሀገር ውስጥ ዜና

በምክትል አፈ-ጉባዔ የተመራው ልዑክ በፓን-አፍሪካ ጉባዔ እየተሳተፈ ነው

By Feven Bishaw

June 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ሎሚ በዶ የተመራው ባለአምስት አባላት ልዑክ ፤ በፓን-አፍሪካ ፓርላማ ጉባዔ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡

ዛሬ በተጀመረው ጉባዔ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር አቶ ሙሣ ፋቂ ማሃማት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ፥ አዳዲስ የአህጉራዊው ምክር ቤት አባላትም ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡