የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራና አፋር ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች የሚስተዋሉ አለመግባባቶችን መፍታት የሚያስችል የሰላም ፎረም ተመሠረተ

By Feven Bishaw

June 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራና አፋር ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች የሚስተዋሉ አለመግባባቶችን መፍታት የሚያስችል አካባቢያዊ የሰላም ፎረም ተመሠረተ፡፡

ፎረሙ የተመሰረተው በወሎ ዩኒቨርሲቲ እና ኢ ኤል አይ ዲ ኤ (ELiDA) ከተባለና በትምህርት፣ በሥርዓተ ፆታ፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በገቢ ማስገኛ፣ በዴሞክራሲ፣ በባህል ግንባታ እና ዘላቂ ሰላም ላይ ከሚሰራ ሀገር በቀል የሲቪል ማህበራት ድርጅት ጋር ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽህፈት ቤት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ነው።