Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አንጋፋው ፀሐፌ ተውኔትና ተዋናይ ሰለሞን አለሙ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አዲ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አንጋፋው ፀሐፌ ተውኔት፣ አዘጋጅ እና ተዋናይ ሰለሞን አለሙ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
በ “አብዬ ዘርጋው” የሬዲዮ ድራማ ይበልጥ የሚታወቀው ሰለሞን አለሙ÷ በአምስት ቋንቋዎች ከ500 በላይ የሬዲዮ ድራማዎችን፣ የመድረክ ቴአትሮችን እና መነባንቦችን ሰርቷል።
ለአብነትም፥ ከዳንኪራው ጀርባ፣ ፍራሽ ሜዳ፣ ገመዱ እና አዙሪትን የመሳሰሉ ተወዳጅ ስራዎች አበርክቷል።
በኢትዮጵያ ሬዲዮ ታሪክ በተለይ ከ1975 እስከ 1980 ገናና ስራዎችን ያበረከተበት ወርቃማ ዘመኑ ነበር።
ሰለሞን በቅርቡ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሌሊቱን ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version