አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ልማት ባንክ በወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የተለያዩ የልማት ዘርፎች ላይ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በአጋርነት እንደሚቀጥል ተገለጸ፡፡
የሥራና ክህሎት ሚንስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ በአፍሪካ ልማት ባንክ የምሥራቅ አፍሪካ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱል ካማራ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገናል ብለዋል፡፡
ባንኩ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በትብብር በሚሠራበት ማዕቀፍ ላይ መወያያታቸውንም ገልጸዋል፡፡
የአፍሪካ ልማት ባንክ÷ በክህሎት ልማት፣ በወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለወጣት ሥራ ፈጣሪዎች የፋይናንስ ድጋፍና ተደራሽነት እንዲሁም በመሰል የትብብር መስኮች ላይ የልማት አጋር ሆኖ እንደሚቀጥል ማረጋገጡንም ነው ወይዘሮ ሙፈሪያት የገለጹት፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!