Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአፍሪካ የመጀመሪያው የክትባቶች ማምረቻ ፋብሪካ በሩዋንዳ ሊገነባ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ከታቀዱት ሦስት የክትባት ማምረቻ ፋብሪካዎች ውስጥ የመጀመሪያው በሩዋንዳ ኪጋሊ ሊገነባ ነው፡፡

የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ እና የባዮቴክ የጥናትና የክትባቶች ማበልጸጊያ ተቋም ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ኡጉር ሳሂን ÷ በኪጋሊ የሚገኘውን የክትባት ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ ትናንት አስጀምረዋል።

የክትባት ማምረቻ ፋብሪካው እስከ ፈረንጆቹ 2024 መጀመሪያ ድረስ የኮቪድ-19 ፣ የወባ፣ የሳንባ ነቀርሳ እና የኤች አይ ቪን ጨምሮ ሌሎች አፍሪካን እያጠቁ ያሉ በሽታዎች ክትባቶችን እንዲያመርት ዕቅድ መያዙ ተመልክቷል፡፡

የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ በትዊተር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት ÷ የፕሮጀክቱ መጀመር ክትባት በፍትሃዊነት ለማዳረስ ታሪካዊ የምዕራፍ መጀመሪያ ነውም ማለታቸውን የዘገበው አፍሪካን ኒውስ ነው።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version