የሀገር ውስጥ ዜና

ተቋማት ለመሰረተ ልማት ግንባታዎች ቁፋሮ ሲያከናውኑ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመናበብ መስራት እንደሚገቸው ተጠቆመ

By Feven Bishaw

June 17, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በግንባታው ዘርፍ የተሰማሩ የግልም ሆነ የመንግሥት ተቋማት ለሚሰሯቸው የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ቁፋሮ በሚያከናውኑበት ወቅት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመናበብ መስራት እንደሚገባቸው ማሳሰቢያ ተሰጠ፡፡

በመዲናዋ በግልም ሆነ የመንግስት ተቋማት የሚሰሩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከመሬት በታች በተቀበሩ የኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ጉዳት እያደረሱ መሆኑን የደቡብ እና ምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክቶች አስታውቀዋል፡፡