የሀገር ውስጥ ዜና

የመተከል እና የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች አጎራባች ወረዳዎች ባህላዊ እርቀ ሰላም ተካሄደ

By Feven Bishaw

June 08, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ1፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የመተከል እና የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች አጎራባች ወረዳዎች ሶስተኛው ዙር ባህላዊ እርቀ ሰላም ተካሂዷል፡፡

በማንዱራ እና ጓንጓ ወረዳዎች የሚገኙት የጨረቃ፣ ባሁስት፣ ዳች ሉምቢያ፣ ዳኋ ማክሰኚት፣ ባቢሳ ቀበሌ ነዋሪዎች እንዲሁም የሁለቱ ወረዳ የፖለቲካ አመራሮች፣ የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት ነው ባህላዊው እርቀ ሰላም በጨረቃ ቀበሌ የተፈፀመው።