የሀገር ውስጥ ዜና

977 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

By Feven Bishaw

June 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29 ፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) 977 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በዛሬው እለት በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ አረቢያ የመመለስ ስራ በአጠቃላይ 977 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል፡፡