የሀገር ውስጥ ዜና

ምናባዊ ንብረት (ዲጂታል መገበያያ ገንዘብ) ህገ ወጥ በመሆኑ ህብረተሰቡ ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠብ ብሄራዊ ባንክ አሳሰበ

By Feven Bishaw

June 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምናባዊ ንብረትን (ዲጂታል መገበያያ ገንዘብ) ለግብይት ወይም ለክፍያ መጠቀም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዕውቅና ያልተሰጠው ድርጊት በመሆኑ ህብረተሰቡ ከእንደዚህ አይነት ሕገ-ወጥ ተግባር እራሱን እንዲጠብቅ ባንኩ አሳስቧል፡፡

የኢትዮጵያ የገንዘብ መደብ ብር እንደሆነና በብሔራዊ ባንክ በሌላ አኳኋን ካልተፈቀደ በስተቀር በሀገሪቱ የሚከናወኑ ማናቸውም የገንዘብ ግንኙነቶች ሁሉ የሚከፈሉት በብር እንደሚሆን የብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 591/2000 በግልጽ እንደሚደነግግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡