የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ህልውናዋ እና ሉዓላዊነቷ አደጋ በተጋረጠበት ጊዜ ሁሉ ችግሮቿን ለመጋፈጥ ፖሊስ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ነበር – ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

By Feven Bishaw

June 05, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ህልውናዋ እና ሉዓላዊነቷ አደጋ በተጋረጠበት ጊዜ ሁሉ ፖሊስ ግንባር ቀደም ተሰላፊ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡

በመስቀል አደባባይ በተካሄደው የፖሊስ አመራርና አባላት የምስጋናና የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰላም ጊዜ በየሰፈሩ በጦርነት ጊዜ በየግንባሩ ሰላም ለማስጠበቅ ደፋ ቀና የሚለው የፌደራል ፖሊስ ከብዙ ድል በኋል ክብረ በአሉን ለማክበር እና ተቋማዊ ስራውን ለህዝብ ለማሳየት በቅቷል ብለዋል፡፡