የሀገር ውስጥ ዜና

“የድርቁ አደጋ የሰው ህይወት ሳይነጥቅ ምላሽ እንደተሰጠ ሁሉ ለዋጋ ንረቱም ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው”- አቶ ሙስጠፌ መሀመድ

By Feven Bishaw

May 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) “የድርቁ አደጋ የሰው ህይወት ሳይነጥቅ ምላሽ እንደተሰጠ ሁሉ ለዋጋ ንረቱም ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው” ሲሉ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ተናገሩ።

ርዕሰ መስተዳድሩ የሶማሌ ክልላዊ መንግስት በክልሉ እየታየ ያለውን የዋጋ ግሽበት በሀገራችን እና በዓለም እያስከተለ ያለውን የዋጋ ንረት ብቻውን ሊፈታው አይችልም ብለዋል።