ዓለምአቀፋዊ ዜና

የሩሲያ ሠራዊት የዩክሬንን ስትራቴጂያዊ ከተማ ሊማንን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ

By Feven Bishaw

May 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያ ጦር ስትራቴጂያዊ ፋይዳዋ ክፍተኛ ነው የተባለችውንና ምስራቃዊቷን የዩክሬን ከተማ ሊማንን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አረጋገጠ፡፡

የሩሰያ ጦር በዩክሬን ምሥራቃዊ ክፍል ዶንባስ ክልል የሚያደርገውን የማጥቃት ዘመቻ አጠናክሮ በመቀጠል የሊማን ከተማ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡