Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ያሰለጠናቸውን ከ2 ሺህ 200 በላይ ተማሪዎች አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና በተከታታይ መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን ከ2 ሺህ 200 በላይ ተማሪዎች አስመረቀ።

ዩኒቨርሲቲው ለ9ኛ ዙር በኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በተፈጥሮ ሳይንስ፣ በማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ክፍል በመጀመሪያ ዲግሪ መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ነው ያስመረቀው።

በምረቃ መርሐ ግብሩ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሀብታሙ አበበን ጨምሮ የዩኒቨርስቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ የሴኔት አባላት፣ የተመራቂ ወላጆችና ቤተሰቦች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

 

Exit mobile version