የሀገር ውስጥ ዜና

ያልተጠናቀቁ የካፒታል ፕሮጀክቶች በ2015 በጀት ዓመት በአነስተኛ ወጪ ለአገልግሎት እንዲበቁ ከፍተኛ ጥረት ይደረጋል – ዶክተር እዮብ ተካልኝ

By Feven Bishaw

May 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2015 በጀት ዓመት አዳዲስ ካፒታል ፕሮጀክቶች ተግባራዊ እንደማይደረጉ እና ያልተጠናቀቁ የካፒታል ፕሮጀክቶችን በአነስተኛ ወጪ በትጋት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማብቃት ከፍተኛ ጥረት እንደሚደረግ የገንዘብ ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ ገለጹ፡፡

የ2015 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት በጀት ባነሰ ወጪ ብዙ ስራ ለማከናወን በሚያስችል ጥብቅ የፊሲካል ፖሊሲ ማዕቀፍ በመመራት እየተዘጋጀ መሆኑንም የገንዘብ ሚኒስትር ደኤታው ተናግረዋል፡፡