ዓለምአቀፋዊ ዜና

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ምክትል አዛዥ በታጣቂዎች መገደላቸው ተነገረ

By Feven Bishaw

May 23, 2022

አዲስ አበባ፣ግንቦት 15፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢራን አብዮታዊ ዘብ አባል እና ምክትል አዛዥ የሆኑት ኮሎኔል ሰኢድ ሃዲ በመኖሪያ ቤታቸው መገደላቸው ተዘግቧል፡፡

ኮሎኔል ሰይድ ሆዳይ በኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ምክትል አዛዥ እና የውጭ ኦፕሬሽን ቡድን አባል ሲሆኑ፥ ቴህራን በሚገኘው መኖሪ ቤታቸው ውጪ መኪና ውስጥ እንዳሉ በሞተር ሳይከል በሚንቀሳቀሱ ሁለት ታጣቂዎች መገደላቸውን የሀገሪቱ ሚዲያ ዘግቧል፡፡