የሀገር ውስጥ ዜና

በክልሉ 218 የንጹህ ውሃና የሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት በቁ

By Feven Bishaw

May 20, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ውሃ መስኖና ማእድን ልማት ቢሮ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 218 የንጹህ መጠጥ ውሃና የሳኒቴሽን ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገለጸ፡፡

በውሃ ፕሮጀክቶቹ ከ411 ሺህ 788 በላይ የክልሉ ህዝብ ተጠቃሚ መሆኑን ቢሮው ጠቅሶ ከተጀመሩ ረጅም አመታት ያስቆጠሩና የህዝብ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እየሰራ እንደሚገኝም አስታውቋል፡፡