የሀገር ውስጥ ዜና

የጀመርነውን የለውጥ ጉዞ ለመቀላቀልና በተሻለ ፍጥነት ለማስቀጠል ዝግጁ ሁኑ- ኢ/ር ታከለ ኡማ

By Tibebu Kebede

March 01, 2020

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አዲስ ተቀጣሪ ሰራተኞች የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ ለመቀላቀልና በተሻለ ፍጥነት ለማስቀጠል ዝግጁ እንዲሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እንጂነር ታከለ ኡማ ተናገሩ።

የከተማአስተዳደሩ ያወጣውን የስራ ቅጥር ፈተና በላቀ ውጤት ያለፋ 8 ሺህ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች ልዩ ልዩ የስራ መደቦች ላይ መመደባቸውን የከንቲባ ጽህፈት ቤት ያወጣው መረጃ ያመለክታል።