የሀገር ውስጥ ዜና

የህንድ ተቋማት አገራቸው ያካበተችውን የዳያስፖራ ተሳትፎ ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ለማጋራት ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ

By Feven Bishaw

April 19, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ህንድ ለረጅም ጊዜ ያካበተችውን የዳያስፖራ ተሳትፎ ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ለማጋራትና በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን የህንድ ተቋማት ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት የዳያስፖራውን ሁለንተናዊ የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ የልምድ ልውውጥ ለማከናወን ህንድ ተገኝቷል፡፡