የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የስቅለትና የትንሳኤ በዓላት በሠላም እንዲከበሩ ዝግጅት ተደርጓል

By Feven Bishaw

April 19, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የስቅለትና የትንሳኤ በዓላት በሠላም እንዲከበሩ ዝግጅቱን አጠናቅቆ ወደ ስራ መግባቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በኮሚሽኑ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር በላይነህ በቀለ እንደገለፁት፥ የስቅለትና የትንሳኤ በዓላት በክርስትና ዕምነት ተከታዮች በድምቀት ከሚከበሩ ሐይማኖታዊ በዓላት ውስጥ ተጠቃሽ ናቸው።