Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነትን በሚመለከት ከሱዳኑ አቻቸው ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአልጀሪያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በአልጀሪያ ከሱዳን አምባሳደር ኤልኦቤይድ መሃመድ ኤልኦቤይድ ጋር በኢትዮጵያና ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል።

በኢትዮጵያና ሱዳን ግንኙነት፣ በሕዳሴ ግድቡ እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ፣ በአህጉራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ውይይት እንደነበርም ተገልጿል።

ውይይቱ ጠቃሚ የሃሳብ ልውውጥ የተደረገበት መሆኑን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version