የሀገር ውስጥ ዜና

መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በመደበቅ በተጋነነ ዋጋ ለመሸጥ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

By Feven Bishaw

March 20, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት የመረጃ ጥናትና ክትትል በማድረግ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት፣ ከፌዴራል፣ ከአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ባካሄደው የተቀናጀ ዘመቻ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በመደበቅ በተጋነነ ዋጋ ለመሸጥ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡

የብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፥ ከመንግሥት የተሰጣቸውን ህጋዊ የአስመጭነት እና የአከፋፋይነት ፈቃድ እንደ ሽፋን በመጠቀም የዋጋ ንረትንና የኢኮኖሚ አሻጥርን በሚፈጥሩ የንግድ ድርጅቶች ላይ ጥብቅና ተከታታይ የመረጃ ጥናትና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል፡፡