የሀገር ውስጥ ዜና

የሰዎች ለሰዎች ድርጅት ለደሴ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ክፍል መሳሪያዎችና ማሽኖሽን ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

March 18, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰዎች ለሰዎች ድርጅት ለደሴ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ክፍል መሳሪያዎችና ማሽኖሽን ድጋፍ ማድረጉ ተገለፀ፡፡

የሰዎች ለሰዎች የዕርዳታ ድርጅት በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት ለደረሰበት የደሴ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 6 ሚሊየን ብር ግምት ያላቸው የቀዶ ህክምና አገልግሎት መስጫ መሳሪያዎችን እና ማሽኖችን በትናንትናው ዕለት ድጋፍ አድርጓል።