የሀገር ውስጥ ዜና

ዩኒሴፍ ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ

By Feven Bishaw

March 18, 2022

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 9 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት የህጻናት አድን ድርጅት ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን የተሟላ የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ፡፡

የድርጀቱ የምስራቅና የደቡብ አፍሪካ ቀጠናዊ ቢሮ የህጻናት ጥበቃ ሪጅናል አማካሪ አንደሪው በሮክስ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስተር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ጋር ተወያይተዋል።