Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በተባበሩት መንግስታት የፀረ-ሙስና ጉባኤ የኢትዮጵያ አፈፃፀም ግምገማ ሪፖርት ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁለተኛው ዙር የተባበሩት መንግስታት የፀረ-ሙስና ጉባኤ የኢትዮጵያ አፈፃፀም ግምገማ ረቂቅ ሪፖርት ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ውይይት እየተካሄደበት ነው፡፡
በጉባኤው ምዕራፍ ሁለት ሙስናን መከላከልና በምዕራፍ አምስት የተመዘበረ ሀብትን ማስመለስ ላይ ትኩረቱን ባደረገው ሪፖርት ላይ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ከፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
የብሔራዊ የቴክኒክ ገምጋሚ ኮሚቴ አባል በመሆን÷ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን፣ ፍትህ ሚኒስቴር፣ ገንዘብ ሚኒስቴር፣ ብሔራዊ ባንክ፣ ፋይናንስና መረጃ ደህንነት አገልግሎት፣ የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ ፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፣ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን እና የመንግስት ግዥ አገልግሎት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version