የሀገር ውስጥ ዜና

አዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች በዜጎች ለሚቀርቡ የአገልግሎት ጥያቄዎች ፈጠን ምላሽ መስጠት አለባቸው – አምባሳደር ብርቱካን አያኖ

By Feven Bishaw

March 05, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ዘመናዊ የአሰራር ስርዓቶችን በመጠቀም ዜጎች ለሚያቀርቧቸው የአገልግሎት ጥያቄዎች ፈጠን ምላሽ መስጠት እንዳለባቸው የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ አሳሰቡ።

አምባሳደሮች በኢምባሲዎች እና ቆንስላ ጽፈት ቤት የሚከናወኑ አገልግሎቶች በሰነድና ዜግነት ማጣራት ምርመራ ሥራ ላይ በቂ እዉቀት፣ ክህሎት እና የተጠናከረ የቡድን ሥራ አስተሳሰብ እንዲኖር እና ስራውን አስተማማኝ ሁኔታ እንዲፈፅም መስራት እንዳለባቸውም አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ተናግረዋል።