የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ አገኘሁ ተሻገር ከወቅቱ የአሴካ ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

March 04, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ከአሴካ (የአፍሪካና የአረቡ አለም አቻ ምክር ቤቶች) የወቅቱ ፕሬዚዳንት ኢናም ማያራ ጋር በኢንቨስትመንት ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ በሞሮኮ ራባት ከተማ እየተካሄደ ከሚገኘው በ11ኛው የአሴካ ጉባዔ ጎን ለጎን የተካሄደ ነው ተብሏል።