የሀገር ውስጥ ዜና

የብልፅግና ፓርቲ 1ኛ ጉባኤውን ሊያካሂድ ነው

By Feven Bishaw

February 28, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልፅግና ፓርቲ 1ኛ ጉባኤውን ከመጋቢት 2 እስከ 4 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡

በጉዳዩ ላይ የብልጽግና ፖርቲ ማዕከላዊ ጽ/ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ እና የፓርቲው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ሙፈሪያት ካሚል፣ ብናልፍ አንዷለምና ተስፋዬ በልጂጌ ዛሬ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡