Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ ተማሪዎቹን አሥመረቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ በተለያየ የህክምና ትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 475 ተማሪዎቹን አሥመርቋል።
ከተመራቂዎቹ መካከል 140 ያህሉ ሴቶች ናቸው፡፡
ሆስፒታሉ የተመሠረተበት 75ኛ ዓመት ክብረ በአልም በዚሁ የታሰበ ሲሆን÷ የኮሌጁ ፕሮቮስት ዶክተር ወንድምገኝ ገዛኸኝ የዘንድሮውን ምርቃት ከምስረታው ቀን ጋር መገናኘቱ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
ምሩቃኑ ከእለቱ የክብር አንግዳ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እጅ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
Exit mobile version