አዲስ አበባ፣የካቲት 18፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በህወሀት የሽብር ቡድን ወረራ ወቅት በሰሜን ሸዋ ዞን ጥቃት የደረሰባቸዉ አካባቢዎች እና አጎራባች ወረዳዎች አሁን ወደመደበኛ እንቅስቃሴያቸው ተመልሰዋል ።
በሰሜኑ ኢትዮጵያ ክፍል የነበረውን ጦርነት ወደመሀል ሀገር የመግፋት እንቅስቃሴ ስልት የነበረዉ የሽብር ቡድኑ ህወሀት እንቅስቃሴ ከወራት በፊት ማክተሙን ተከትሎ የሽብር ቡድኑ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ከተሞች መደበኛ እንቅስቃሴን ጀምረዋል፡፡